፻ ዘመን ተሻጋሪ • ISO 21001:2018 Certified
ለነባር እና ለአዲስ ሰልጣኞች የተዘጋጁ ዋና ዋና ማሳሰቢያዎች
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የነባር ሰልጣኞች ምዝገባ ከመስከረም 12 እስከ መስከረም 23 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ይካሄዳል። በወቅቱ ተገኝታችሁ እንድትመዘገቡ እናሳስባለን።
በመደበኛው የምዝገባ ጊዜ ያልተመዘገቡ ነባር ሰልጣኞች ከመስከረም 26 እስከ መስከረም 30 ቀን 2018 ዓ.ም የቅጣት ክፍያ በመክፈል መመዝገብ የሚችሉበት የመጨረሻ ጊዜ ነው።
ለነባር ሰልጣኞች የ2018 የትምህርት ዘመን የመጀመሪያ ዙር መደበኛ ትምህርት በጥቅምት 3 ቀን 2018 ዓ.ም ይጀምራል።
በ2018 የትምህርት ዘመን በኮሌጃችን የተመደባችሁ አዲስ መደበኛ ሰልጣኞች ምዝገባና ማጣሪያ ከጥቅምት 10 እስከ ጥቅምት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። አስፈላጊ የትምህርት ማስረጃዎችን ይዛችሁ እንድትቀርቡ እናሳውቃለን።